የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

@bahiretibebat


የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ጥናት እና ምርምር ጽሁፎች የታተሙ ያልታተሙ ጆርናሎች ችግር ፈቺ ሀገራዊ እና ዓለማቀፋዊ ዳሰሳዎች መጽሐፎች ይቀርቡበታል

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

15 Oct, 17:50


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

15 Oct, 16:44


-በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩና የሆኑ አባቶች ጳጳሳት የጻፏቸው መጻሕፍት በከፊል፡፡ አባቶች አንዱ አገልግሎታቸው መጻሕፍት መጻፍ ነው፡፡ መሆንም አለበት፡፡

1. ፍኖተ እግዚአብሔር በብፁዕ አቡነ ቶማስ

2. ፍኖተ ሕይወት በብፁዕ አቡነ ማትያስ

3. ይግባኝ ለክርስቶስ እና ዓለም ጉድ ወለደች በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

4. ኅብረ ብዙ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስ

5. ርትዕት ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ገብርኤል

6. ኮሮና ኤልያስ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስ

7. መሠረተ እምነት ለሕጻናት በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

8. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

9. የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

10. ብጹዓን ገባርያነ ሰላም በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

11. ነገረ መንፈስ ቅዱስ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

12. ፈለገ አሚን ዘኦርቶዶክስ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

13. ፍኖተ ሕይወት በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

14. የኢትዮጺያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዘመናቱ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

15. የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

16. ሥረወ ሃይማኖት ብፁእ አቡነ ማቴዎስ የኢየሩሳሌም የምስካየ ኅዙናን የበአታ ሊቀጳጳስ የነበሩ

17. ሀልወተ እግዚአብሔር በዘመናት በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

18. ድሕነት እና ኢትዮጵያ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

19. የሃይማኖት መቻቻል በኢትዮጵያ አለን? በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

20. ግብረ ሰዶማዊነትና የኃጢአት ደመወዝ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

21.መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ በፖትርያርክ ብፁእ አቡነ ቴዎፍሎስ

22. “Filsata: The Feast of the Assumption of the Virgin Mary and the Mariological Tradition of the Ethiopian Othodox Tewahedo Church” በፓትርያርክ ብፁእ አቡነ ጳውሎስ

23. ዜና ሕይወቱ ለቅዱስ ጳውሎስ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

24. ስለ እግዚአብሔር መኖር በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

25. ትምህርተ አበ ነፍስ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

26. ክብረ ድንግል በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

27. ድንግልናዊ ሕይወት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

28. የእግዚአብሔር ሕገ መንግሥት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

29. እንጸልይ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

30. ማኅበራዊ ኑሮ በኢትዮጵያ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

31. ጥንታዊ የኢትዮጵያ ትምህርት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

32. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት እና ትምህርት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

33.ትምህርተ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ገሪማ

34.Monasticism and ascetic life in Ethiopia በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

35. ክብረ ቅዱሳን በብፁዕ አቡነ ገብርኤል

36.ትምህርተ ክርስትና በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

37.ግብረ ሕማማት በአቡነ ያዕቆብ

38.ፍኖተ ቅድስና በአባ ማትያስ

39.ፍሬ ጸሎት ወንስሐ በአቡነ ኤጲፋንዮስ

40.ፍኖተ ሃይማኖት ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን በአማርኛ እና በኦሮምኛ አብነ ኤጲፋንዮስ

41.ክህነት አገልግሎት በአማርኛ እና በኦሮምኛ በአብነ ኤጲፋንዮስ

44.ከጥንት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የሃይማኖተ አበው አስተዋጽዖ በአብነ ኤጲፋንዮስ

45.መጽሐፈ ጸሎተ ሱባዔ በአባ ሳሙኤል

46.ሲኖዶሳዊው ጉዞ በኦርቶዶክሳዊ ቀኖና ሲመዘን በብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ

47.የምሥጢራት ቁልፍ በብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ

48.መጽሐፈ በቁዔት ዘጾም ወዘበዓል (1946) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

49. ርትዕት ፍኖት ዘባስልዮስ በባሕረ ጣና (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

50. የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ትርጓሜ (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

51. ቃለ ምዕዳን (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

52. የሐዋርያት ሥራ ትርጓሜ፣ የሰባቱ መልእክታትን ትርጓሜ እና የዮሐንስ ራእይን ትርጓሜ (1951) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

53.ቃለ ምዕዳን (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

54.መዝገበ ሃይማኖት (1950) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

55.ኦርቶዶክሳዊ የስብከት ዘዴ በብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

56.ፍኖተ ቤተ ክህነት ወቤተ መንግሥት በአቡነ ሕርያቆስ

57.The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. An Integrally African Church. በአቡነ ይስሐቅ

-ያልተጠቀሰ ካለ ይጠቁሙን፡፡ አሻሽየ ያዘጋጀሁት ጽሑፍ ነው።

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

14 Oct, 19:09


ወንድሜ ሰውነትህን ዘወትር ዝለፋት፡፡ ከሥጋ የምትለዪበት፣ የምታልፊበት ጊዜ ደርሷል በላት፡፡ ኋላ ጥለሽው በምትሔጂ ሥራ ዛሬ ለምን ደስ ይልሻል? እሱን በማየት ጥቂት ዘመን ተድላ፣ ደስታ የምታደርጊበት ኋላ ብዙ ዘመን በምታጭው የቀድሞ ሥራሽን ዕወቂ።

የሠራሽው ሥራ ምንም እንደሆነ አስቢ፡፡ ያለ ዘመንሽን ከማን ጋር ፈጸምሽው? ከጌታ ጋር ነው፣ ከሰይጣን ጋር ነው? ደክመሽ የሠራሽውን ማነው ሚቀበልሽ? ጌታ ነው፣ ወይስ ስይጣን ነው? በጊዜ ሞት ሊዋሐድሽ የሚመጣው ማነው? በመንግሥተ ሰማይ አርፈሽ ትኖሪ ዘንድ በሥራሽ ደስ ያለው ማነው? ለማን ብለሽ ደከምሽ? ለማን ብለሽ መከራ ተቀበልሽ? ለመንግሥተ ሰማይ ብለሽ ነው ወይስ ለገሃነም ብለሽ ነው? ደስ ብሎሽ ታገኚው ዘንድ አኳኋንሽ ምንድን ነው? ነፍስሽ ከሥጋሽ በተለየች ጊዜ በመንግሥተ ሰማይ ይዋሐድሽ ዘንድ ገንዘብ ያደረግሽው ምንድነው? በማን እርሻ ላይ ሊያውሉሽ ተቃጠሩሽ? የምትለይበት ፀሐይ ዕድሜሽ በገባ ጊዜ ዋጋሽን እሰጥሻለሁ ያለሽ ማነው? ጌታ ነው፣ ዲያቢሎስ ነው?

ነፍሴ ሆይ! ሰውነትሽን መርምሪ። ዕጣሽ በማናቸው ቦታ እንደሆነ ዕወቂ፡፡ እያዘንሽ እየተቆረቆርሽ አልቀሺ፤ ለምኚ፡፡ ክቡራን መላእክት ደስ በሚላቸው ገንዘብ ደስ ይላቸው ዘንድ አንደበትሽ እየፈራ ያመስግን፡፡ ግራ ቀኝ ፊትሽን በዕንባ እጠቢው፤ መንፈስ ቅዱስ ያድርብሽ ዘንድ ከኃጢአት ይለይሽ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እያለቀሽ ለምኚ፡፡ የልቅሶ ዜማ ያስተምሩሽ ዘንድ ማርያምንና ማርታን ጥሪያቸው፡፡ አልዐዛር ብሎ ያለቀሰ ጌታ ያዝንልሽ ዘንድ ለምኚ፡፡ ራርቶ ለብዙ ሰዎች ወደ አለቀሰ ጌታ "ምርር ብዬ ያለቀስሁትን ለቅሶዬን ተቀበልልኝ'' እያልሽ ወደሱ አልቅሺ፡፡ በመልዕልተ መስቀል በተቀበልከው መከራ ከደዌ ኃጢአት አድነኝ፡፡ በመስቀል ላይ በቆሰልከው ቁስል ከቁስል ኃጢአት አድነኝ፤ ደሜን በደምህ አንጻው ብለሽ ለምኚ፡፡

(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ ገጽ 25-26
በዲያቆን ሞገስ አብርሃም፣ ውዳሴ አምላክ ዘዘወትር)

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

13 Oct, 17:32


“ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና። ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ #የጨለማውን_ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር ☀️ እንልበስ። በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ 👉በዘፈንና 👉በስካር #አይሁን፥ 👉 በዝሙትና 👉በመዳራት #አይሁን፥
👉በክርክርና 👉በቅናት #አይሁን፤ ነገር ግን ጌታን #ኢየሱስ_ክርስቶስን_ልበሱት ፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።”
— ሮሜ 13፥11-14

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

10 Oct, 16:22


ቁርጥ ህሊና

ሃይማኖተ ወንጌል #ቁርጥ_ህሊናን ትሻለች።ወጪ ወራጅ በሆነ ፈቃድ ፈጽማ አትሠራም።ቁርጥ ህሊና የሚመጣው በዓለመ መንግሥተ ሰማያት ከሚያገኘው #ተስፋ የተነሣ ነው።
ከእግዚአብሔር የተረገረን ተስፋ የማያሳፍር እስከሆነ ድረስ በቁርጥ ፈቃድ ህሊናን በተስፋው ሰቅሎ ለመኖር ያበቃል።
መድኅነ ዓለም #ክርስቶስ በፈቃዱ በመስቀል ተሰቅሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው እንደለያት በቁርጥ ህሊናም #ወጪ_ወራጅ_ህሊናን በቁርጥ ተስፋ እንለይባታለን።"የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ #ሥጋን_ከክፉ_መሻቱና_ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።"ገላ.፭፥፳፬ብሎ ፍጹም ሐዋርያ እንደነገረን።
👉 ቁርጥ ህሊና የመስቀል ሕይወት ልምምድ ነው። ወይም ለባሴ መስቀል ሁነው በሕይወተ ወንጌል ሲመላለሱ የሚገኝ ጸጋ ነው።
በቅድስት ጥምቀት እና በጥሙቅነት አኗኗር ክርስቶስን ስንለብሰው ስንመስለው በበጎ ፈቃድ ላይ ቁርጥ ህሊና ትጸናለች፦ "ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋል።"ገላ.፫፥፳፯ ብሎ ለባሴ ክርስቶስ ሐዋርያው እንደአስተማረን።
ክርስቶስን የለበሰ ሰው ሌላ የበለጠ ምድራዊ ነገር ኑሮ ቁርጥ መስቀላዊት ህሊናውን አያውከውም።
በተቀደሰቸው #ርትዕት_ቁርጥ_ሀልዮ ውስጥ፦
➭ ተዘክሮተ እግዚአብሔር፣
➭ ተዘክሮተ መስቀል፣
➭ ተዘክሮተ ሞት፣
➭ ተዘክሮተ ትንሣኤ፣
➭ ተዘክሮተ ፍትህ ርትዕ
➭ ተዘክሮተ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት ትገኛለች።
👉ፍትህ ርትዕት የትሩፋት ሁሉ ማከናወኚያ የቁርጽ ህሊና መዳረሻ ናት።
ነፋስ ከአፋፍ ፣ነገር ከአፍ እንደ ማይጠፋ ከርትዕት ሀልዮም ቁርጥ ህሊና አይጠፋም። ° ህውኩ ልቡና ግን ከጸጋ እግዚአብሔር ይርቃል።"ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው።"ያዕ.፩፥፯ ብሎ አባታችን ያዕቆብ እንዳስተማረን።
"ማመን ከሆድ መታጠብ ከክንድ" የሚባለውም ለዚያ ነው። የአፉ ሌላ የልቡ ሌላ ያልሆነ በቁርጥ ፈቃድ እና በመስቀላዊት ህሊና የተሰቀለ ሰው ወንጌል ዕውቀት ሳይሆን ሕይወት የሆነችው ሰው ነው።
በዚህ መንገድ ሃይማኖተ ወንጌል ዕውቀት ብቻ ሳይሆን #ሕይወትም ሁና በሕይወተ መስቀል ስታኖረን ቁርጥ ህሊና ይጸናልናል። በምድር በተናቀ ሕይወት በሰማይ በከበረ ጸጋ ለመኖር ቁርጥ ህሊና ያስፈልጋል። ነቢይ በመዝሙሩ፦"ልቤ ጨካኝ ነው አቤቱ ልቤ ጨካኝ ነው እቀኛለሁ እዘምራለሁ።"መዝ.፶፮፥፯ ያለው በቁርጥ ህሊና ውስጥ ሁኖ ስለሚፈጽመው አምልኮት ነው።ልቤ ጨካኝ ነው ማለቱ ማንም ምንም ከቁርጥ ህሊናየ አያወጣኝም አያናወጠኝም ማለቱ ነው።
በመስቀል ለመኖር 'መችም፣የትም፣እንዴትም' ቁርጥ ህሊና ያስፈልጋል።
👉 በወንጌል ምድር ላይ የተተከለ ጹኑዕ ፈቃድ፣በቀራንዮ መስቀል ላይ የተሰቀለ ቁርጥ ህሊና የክብር ፍሬን ያፈራል።"ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራችኋል።"ዮሐ.፲፭፥፰ እንዲል።
ፍሬ ሥጋ #በሞት ይነሣል።ፍሬ ወንጌል ግን #በትንሣኤ_ዘጉባኤ እጽፍ ድርብ ሁኖ ይመለሳል።

ከመ/ር ገ/መድኅን እንየው

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

08 Oct, 13:36


“ወደ #አንተ_እንዳይቀርቡ በልባብና በልጓም ጉንጫቸውን እንደሚለጕሙአቸው፥ #ልብ_እንደሌላቸው እንደ ፈረስና እንደ በቅሎ አትሁኑ።”
  — መዝሙር 32፥9

“Be ye not as the horse, or as the mule, which have #no_understanding: whose mouth must be held in with bit and bridle, lest they come near #unto_thee.”
  — Psalms 32፥9 KJV

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

08 Oct, 06:14


"እኛን ስለማዳን ተሰቀለ። በመስቀሉም ሕይወታችን፣ ቤዛችን እና ጽንዓችን ሆነልን። ይኸውም የማያልቅ ደስታ ያለበት ረቂቅ ምሥጢር ነው። የሰው ነፍስ ሁሉ ይህን ይዛ ብትገኝ ከእግዚአብሔር የሚለይ ክፉ መኞት ከዚህ ደስታ ሊለያት አይችልም።"
ትምህርተ ኅቡኣት

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

07 Oct, 14:18


የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡

መጽሐፈ አርጋኖን - ዘሰኑይ

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

06 Oct, 19:22


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

06 Oct, 05:54


ፈሪሳዊነት

https://youtu.be/Dh1Ssdk5HrM?si=lVwKnrIYraZvrYNI


#ዲያቆን_ብርሀኑ_አድማስ

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

05 Oct, 12:49


ዋቅ ኤፈና ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጋር ቁርኝት አለው? የማሕበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር መጽሔት ቁጥር 2 ያሳተመውን ጥናታዊ ጽሑፍ እንመልከት።

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

05 Oct, 11:52


ሥርዓተ ማኅሌት
አመ ፳ወ፮ ለመስከረም ዘቀዳማይ ጽጌ በዓለ ቶማስ ወሀብተማርያም ማህሌት
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም፤ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም፤መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢ ዓለም፤ወልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም፤እምአምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም።

ዚቅ፦
ለሥሉስ ቅዱስ ጥዑም ቃሎም፤ናርዶስ ጸገየ ዉስተ አፍሆሙ፤

መግቢያ ዘማኅሌተ ጽጌ

ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤ተሠርገወት ምድር

(🌹#በህብረት_ሁሉም🌹)
በስነ ጽጌያት፤ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት።

ማኅሌተ ጽጌ፦
ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ እምዓጽሙ፤ለዘአምኃኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤ወበእንተዝ ማርያም ሶበ ሐወዘኒ ጣዕሙ፤ለተአምርኪ አኀሊ እሙ፤ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡

ወረብ
መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ/፪/
ወበእንተዝ ማርያም አኅሊ ለተዓምርኪ/፪/

ዚቅ፦
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ፤ ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ፤ ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዓቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ፤ለዕረፍት ሰንበት ሠራዕከ፤

ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፣ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ወረብ
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ /፪/
አመ ቤተ መቅደስ ሠናይትየ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ/፪/

ዚቅ፦
ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ፤እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ፤መላእክት ይትለአኩኪ፣ፃዒ እምሊባኖስ ስነ ሕይወት

ማህሌተ ጽጌ
ጽጌኪ ማርያም ኮነኒ ሲሳየ ወአራዘ፤ወጸግወኒ እምትካዝ ተአምረኪ መናዝዘ፤ቶማስ ሎቱ አመ ገቦሁ አኃዘ፤እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ፣ረከበ በውስተ ቁስሉ አፈወ ምዑዘ

ወረብ-
አመ ገቦሁ ቶማስ ሎቱ አኃዘ/፪/
እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ ረከበ አፈወ ምዑዘ/፪/

ዚቅ-
ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወልድ እኁየ ፈነወ ዕዴሁ እንተ ስቊረት፤ለከፎ ሶቤሃ ርስነ መለኮት

ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፤አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ/፪/

ዚቅ
ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት፤ ወስብሕት በሐዋርያት፤አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ፤ ወትምክህተ ቤቱ ለ፳ኤል።

ሰቆቃወ ድንግል
በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕፀተ ግጻዌ ዘአልቦ፤ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤ወይሌ ወላህ ለይበል ዘአንቦ፤ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ሶበ ለኩለሄ ረከቦ፤ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ

ወረብ፦
ከማሀ ኀዘን ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ኀዘን/፪/
ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ ዓይነ ልብ ዘቦ/፪/

ዚቅ፦
እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ፤ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በዉስተ ኩሉ ዘረከቦ፤

መዝሙር

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ትዌድሶ መርዓት፤እንዘ ትብል ነዓ ወልድ እኁየ፤
ንፃዕ ሐቅለ፤ትዌድሶ መርዓት ንርዓይ ለእመ ጸገየ ወይን፤ወለእመ ፈረየ ሮማን፤ትዌድሶ መርዓት አሠርገወ ሰማየ በከዋክብት፤ወምድረኒ በስነ ጽጌያት፤ትዌድሶ መርዓት
እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ፤እግዚአ ለሰንበት፤ማ፦ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ፤
ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም።

አመላለስ፦
ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ/፪/
ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም/፬/
ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤
በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14

እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን

ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በረሀብ በስደት ስላሉት እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት እንጸልይ
የሰላም የምህረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምህረቱን ቸርነቱን አይንሳን

አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዘዝዋይ ገዳም
መስከረም 25/1//2017
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

05 Oct, 09:25


ሐዋርያት 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² ጳውሎስም በአርዮስፋጎስ መካከል ቆሞ እንዲህ አለ፦ የአቴና ሰዎች ሆይ፥ እናንተ በሁሉ ነገር #አማልክትን እጅግ እንደምትፈሩ እመለከታለሁ።
²³ የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ፦👉 #ለማይታወቅ_አምላክ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና፦ እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ።
²⁴ #ዓለሙንና_በእርሱ_ያለውን_ሁሉ_የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤
²⁵ እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም።
²⁶-²⁷ ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ፥ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጥናትና ምርምር መጽሔት ስራዎች

05 Oct, 09:24


አንድ ወዳጄ አሁን እንዲህ አለኝ:

ኢሬቻ የዋቄፈታ “ሃይማኖት” ሥርዓተ አምልኮ ነው ይባላል ያው የተለያዩ ባህላዊ ነገሮችንም ቢይዝም ማለት ነው..

እንዲያ ከሆነ እዚህ ቦታ ላይ ክርስቲያን ምናልባት ከተገኘ ሊገኝ የሚገባው:

“ይህ እናንተ ዓለምን የፈጠረ ‘ዋቃ’ የምትሉት የማታውቁት አምላክ የጌታችን ኢየሱስ አባት ነው.. ሁላችንን ከሞት ያድነን ዘንድ ልጁን ላከው.. እርሱም ስለሁላችን ሞቶ ተነሣ.. ስለዚህ እኛም ሞተን እንደማንቀር እርግጥ የሆነ ተስፋን ሰጠን.. ከሞት ታመልጡ ዘንድ በልጁ በኢየሱስ እመኑ..”

ብሎ ለመናገር መሆን አለበት አለኝ.. እንዴት ነው ያስማማል..??

@Apostolic_Answers

4,305

subscribers

529

photos

24

videos