👉12,907 ወገኖች ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተመልሰዋል
★ ከአህጉረ ስብከት ሪፓርት የምንጠብቀው ይህንን የምስራች ነው።★
« ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ»1ቆሮ 9÷16
ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ሐምሌ 9 ቀን 2015 በመንፈስ ቅዱስ ምርጫና በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ለታላቅ ሐዋርያዊ አገልግሎት ከተመረጡ ሊቃነ ጳጳሳት መካከል አንዱ ናቸው። እኚህ አባት ከጵጵስና በፊት በነበራቸው ለወንጌል የተሰጠ ሕይወት የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስን ክብር በድንቅ የአገልግሎት ጸጋ ያለ እረፍት ሲሰብኩ የኖሩ ታላቅ የወንጌል ገበሬ ናቸው።በእግዚአብሔር ፈቃድ ወደ ላቀው ሐዋርያዊ አገልግሎት ተጠርተው ቅድስት ቤተክርስቲያን የጵጵስና አደራ ስትጥልባቸው የልባቸው ናፍቆት፣የአንደበታቸው ጣዕም፣የነፍሳቸው እርካታ የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን በገጠር በከተማ ዞረው በመስበክ በተለይም በኦሮምኛ ቋንቋ የክብሩን ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ስልጣን በማወጅ ብዙዎችን ወደ ክርስቶስ ፍቅር ወደ እናት ቤተክርስቲያናቸው ጉያ ሰብስበዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በከፍተኛ ሁኔታ ቁጥራቸው እየተመናመነ በሚገኝበት ምዕራብ ሸዋ ላይ ከተመደቡበት ጊዜ ጀምሮ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የወንጌል አገልግሎት በመስጠትና አገልጋዮች ተግተው ሕዝብን ማዕከል ያደረገ የወንጌል አገልግሎት በስፋት እንዲሰጡ ጠንካራ መመሪያ በመስጠትና ዝቅ ብለው በማገልገል በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት 12,907 የሚሆኑ ወገኖችን አስተምረው በማጥመቅ ወደ ቀደመችው እናት ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲመለሱ በማድረግ የሚያስደንቅ ተግባር ፈጽመዋል።በርካታ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ከፍተው አገልግሎት አስጀምረዋል፣ለበርካታ ብቃትና ጥራት ላላቸው ደቀ መዛሙርት ማዕረገ ክህነት በመስጠት ሕዝባቸውን በቋንቋቸው እንዲያገለግሉ ከመንፈሳዊ አደራ ጋር አባታዊ መመሪያ በመስጠት ለሕዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት እንዲሰጥ ትልቅ ሚናን ተጫውተዋል አሁንም በትጋት እየሰሩ ይገኛል።
በብፁዕነታቸው ብርቱ ጥረት የክርስትና እምነት በምዕራብ ሸዋ ላይ እንደ አዲስ እያበበ የመጣ ሲሆን በርካታ ወጣቶች ወደ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እየተመለሱ ነው።ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በዓለ ሲመታቸው በመብል በመጠጥ እናስብሎት ሲባል አይሆንም ሙሉ ወጪውን ለወንጌል አገልግሎት አውሉት በማለት ቁርጥ ውሳኔ በማስተላለፍ ታላቅ ጉባዔ ተዘጋጅቶ በስብከተ ወንጌልና በዝማሬ ብዙ ሕዝበ ክርስቲያን በቃሉ በረከት እንዲያሳልፈው አድርገዋል።
የጳጳሳት ሹመት ዋነኛ ዓላማ የክርስቶስን ወንጌል በኃይልና በሥልጣን በመስበክ ነፍሳትን ወደ ጸጋው ዙፋን መማረክ ስለሆነ ሌሎች ብፁዓን አባቶችም የተጠሩበትን የወንጌል ዓላማ ከምንም በላይ ትኩረት ሰጥተው በመሥራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ምርኮን በመበዝበዝ መላካሙን የምሥራች በሪፓርታቸው እንዲያሰሙን በተስፋ እንጠብቃለን።
ብፁዕ አባታችን አቡነ ገብርኤል ሆይ ! የተጠሩለት ዓላማ የክብሩን ወንጌል በማወጅ ትውልድ የልጁን መልክ ይመስል ዘንድ ማነጽ ነውና የቆሙለትን ዓላማ በጥብዐት በመፈጸም ለብዙዎች አርአያ በመሆን የቤተክርስቲያንን ክብር ወደ ላቀ ከፍታ እንደሚያሻግሩ ጽኑ እምነታችን ነው።
የብፁዕ አባታችን አቡነ ገብርኤል ቡራኬና ጸሎት ትድረሰን
መ/ር ታሪኩ አበራ
Galanni Waaqayyoof Haa Ta'u!
✝️
✥✥✥✥✥✥✥✥✥
✥••┈••●◉✞◉●••┈••✥
💻©Katamaa Baayisaa✍️
#Tulluu_Jireenyaa_Jalaa
⛪️Asallaa💒
✥••┈••●◉✞◉●••┈••✥
✥✥✥✥✥✥✥✥✥
✝️
FB Page:-https://www.facebook.com/profile.php?id=100090278975719
Farniture Page:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558960356681
Telegram:- https://t.me/AgartuOrthdoxMedia
Telegram2nd:- https://t.me/AgartuOrthodoxMediya
FB Page:-https://www.facebook.com/profile.php?id=100077746210793&mibextid=ZbWKwL
Whatsapp:- https://chat.whatsapp.com/CjpmvlLoAh84DA0Ntj1LNU
Chaanaalii Whatsapp:- https://whatsapp.com/channel/0029VaEQ5feEFeXlBReM9J0L
Tiktok:- tiktok.com/@agartuorthodoxmedia
WEBSITE:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100077746210793
Instagram:- https://www.instagram.com/invites/contact/?i=1oiq6gs7xizj1&utm_content=n6qenn8
Twitter:- https://twitter.com/ketemab278?t=DydF9n4cmJQ7HSuh93C2TQ&s=09
Gmail:- [email protected]
Yuutubii:- https://youtube.com/@Agartuortomedia
Signal:- https://signal.org/install
Viber:- https://vb.me/letsUseViber
Imo:- https://call.imo.im/Agartuorthodoxmedia
Botim :- +251910637055
Call 📞 +251910637055
#Horaa_Bulaa
#Deebanaa
#Wanta_gaarii_gochuu_warra_kaaniin_ga’uus_hin_dagatinaa! Waaqayyoo aarsaa akkasiitti ni gammada. (Ibr 13:16)
#Afaan_koo_hamaa_hin baasu_arrabni_koos _soba_hin_dubbatu.(Iyo.27:4)