አብሮነት/Abronet

@abronet_ethiopia


አብረን ስንሆን ያምርብናል!!

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 23:49


እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ 🙏

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 23:45


ቀለድሁና ሳቅ ብትል
ደማም አፏ፥
እንደበቃ ባህታዊ፥
(የረቀቀውን አጉልቶልኝ
የጠበበውን አስፍቶልኝ)
ጠሐይቱ ከዓይኖቿ ማይ፥
ተነካክራ ተለቃልቃ ፥ ስትመለስ ወደሰማይ፥
ዐየሁና... ዐየሁና...

በልጅነት በውብ ዘመን ፥ ድሮ እንደሰሙት ሙዚቃ፥
ሆድ ውስጥ ያለ ባር ባር የሚል ፥ ከሰመመን የሚያነቃ፥
የሚመስል፥
በአሳሳቋ ንፅህና፥
የረሳሁትን መኖር ፥ ደሞ ደሞ አስብና፥
እናፍቅና... እናፍቅና...

አሳሳቋ፥
ከዐይኖቿ ጋር ቅንብሩን፥
የተሳካ ስብጥሩን፥
ፊት ገጿ ላይ የሚራቀቅ ፥ የተፈጥሮን ፍልስፍና፥
አጠናና... አጠናና...

"ትንኝ ልሁን?
ተወርውሬ ፥ ከብሌኗ ስር ልወተፍ?
የዓይኖቿን በር ደጅ ልጥና?
ይለይለት ሞት ይውሰደኝ ፥ ጨው እንባዋን ልጠጣና?"
እል እልና...

አሳሳቋ እንደባህር ዛፍ ፥ ሌላ ቁንጅና ሲገድል፥
ጎኗ ያለውን ውበት ሁሉ ፥ የሌላ ማማር ሲያጎድል፥
የብቻዋን ልዕልና
እታዘብ... እታዘብና...

ከሳቋ ፊት ተቀምጬ
አያታለሁ... አያታለሁ
"ምንሆንክ?"ስትል
"ቀልድ በሆንሁ" እላታለሁ

ቀልድ ልሁንልሽ?
ገጣሚ ሚኪ ምናሴ

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 23:33


🌙⭐️ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ⭐️🌙

መልካም በዓል ይሁንላችሁ❗️
አብሮነት🙏

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 23:04


አብሮነቶች   ለድንቁ አዘጋጅና ተዋናይ ኩራባቸው ደነቀ ቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመድ   ለአድናቂዎቹ  ሁሉ  መፅናናትነ ይሰጣቸው ዘንድ ይመኛል  
ነፍስ ይማርልን
አብሮነት

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 23:04


" ቁርስ ስጡኝ አለ ። ሰርተው ሲያቀርቡለት ግን ሕይወቱ አልፏል "
***
     
  ይህ የአርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የዛሬ ሕይወት ነው ። ትናንት ከወዳጆቹ ጋር ሰላማዊ ግንኙነቱን ፈጽሞ ነው የገባው ። ዛሬ ጧትም ሰላማዊ ነበር ። ጧት አልጋ ላይ ሆኖ ቁርስ እንዲያዘጋጁለት ተናገረ ። ቁርስ አዘጋጅተው መኝታ ቤቱ ገብተው ሲቀሰቅሱት ግን በሕይወት የለም ። በቃ ! ይህ ነው የኩራ መጨረሻ ። ይኸው ነው የማናችንም ሕይወት ። ቁርስ ተሰርቶ እስኪቀርብ እንኳ ፋታ የማይሰጥበት ዓለም ።

     የሦስት ልጆች አባት የነበረው ኩራባቸው ደነቀ ነገ ከ5:00 - 6:00 በቀጨኔ መድኃኒዓለም ስርዓተ ቀብሩ ይፈጸማል ።
🖊ቴዎድሮስ ተክላረጋይ

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 22:44


{የምነግራትን አታምንም እንጂ..}
:
የወደደችው እንደሚከዳት፥
የከዳችው ሰው እንደሚወዳት
ያመነችው ሰው ሄዶ እንደሚቀር፤
የጠሉትም ሰው እንደሚፈቀር።

የምነግራትን አታምንም እንጂ..
:
ሲያብለጨልጩ አምረው ሚታዩ
ስሜቶች ሁሉ እንደማይቆዩ
የመልክን ውበት የተቃመሱ
እድለኛ አይኖች እንደሚያለቅሱ
ፍቅርን በጣምራ የሚዘምሩ፤
ኋላ ለየቅል እንደሚቀሩ።

የምነግራትን አታምንም እንጂ..
:
የሚያለቅስ ሁሉ ንፁህ እንዳይደለ
የሚስቅ ሁሉ እንዳልበደለ
ወደው የራቁት  ሰው ቢናፍቅም
የቆየ ሁሉ  እንደማይጠቅም

የምነግራትን አታምንም እንጂ..
:
የሚዘንብ ሁሉ ሰርክ አይዳምንም፥
ሰባኪ ሁሉ ወንጌል አያምንም።
በደስታም መሃል ይሰማል መርዶ፥
የሚሳም ሁሉ አይደል ተወዶ፤
የጥልቁ አይደል የጽድቅ ስንኩል፥
መጠንቀቅ አለ በእግዜርም በኩል።

ህይወት አይደለች ~ ምታስባትን
አለም አይደለች  ~ የሰበኳትን፤
አታምንም እንጂ : የምነግራትን።

@mikiyas_feyisa

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 22:24


በጎፋ በደረሰው አደጋ እያዘንን የሞቱት ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን ፣ ለዘመዶቻቸውን እንዲሁም ለመላ ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ወገኖቻችንም መፅናናትን እንመኛለን ።
🙏ፈጣሪ ከክፉ ነገር ይጠብቀን
           #   አብሮነት

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 21:58


#ወደ_ግጥም__ወደ_ነብይ
ፈግታን ስለቸረን መነሱ ___ ስላስጠለለን ዋርካነቱ
ስለ አፅናኝ ጨዋታዎቹ ___ ሕይወት ስለሚያሞቁ ግጥሞቹ
ቅንነቱን ለማቀንቀን ___ አባትነቱን ለማወደስ
ስለ ግጥም _ _ _ ደግሞም ስለ ነብይ
ቅዳሜ እንሰበሰባለን። ፈንድቃ ቤተ ጥበብ [ ፈንድቃ የጥበባትና ባህል ማዕከል:Fendika Art & Cultural Center ]

• ውብ ግጥሞች ልዩ
• ልዩ የሙዚቃ ጨዋታዎች
• ነገረ ነብይ
• የጥበብ ቅማ ቅመም

የምትወዷቸው የምንወዳቸው ሁሉ አሉ። ስለ ግጥም _ ስለነብይ።

ከ8:00 ቀደም ብላችሁ ኑ።
ቡናውም ጨዋታውም ወዳጅ ትውውቁም እንዳይቀርባችሁ።

ቅዳሜ ሀምሌ 6 2016 ዓ.ም 😍🙏🙏🙏😍

@getem
@getem

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 21:50


እኔና ቤቴ
.
( ሰሎሞን ንጉሱ )
.
በዘመመ ህይወት
በደሳሳ ቤቴ
የለሁም እንደ ሰው
አለሁ እንደ ቤቴ
የግድግዳው ቀለም
ህይወቱ ተነትቦ
የጥበብ ቀለማት
ወዘናን ተርቦ
ያ..! ውብ የ'ሱ ቀለም
አሁን ግድግዳው ላይ
በህይወት ላይ የለም፡፡
.
ነፍስ ይማር ለ'ሱ
ባካል ላለው ሥጋ ለሞተው መንፈሱ
ቀለሙ ተነትቦ የህይወት ግድግዳው
አለሁ በግድግዳው በህይወት ሰሌዳው፡፡
..
እኔም እንደ ቤቴ
በዘመመ ህይወት
በደሳሳ ቤቴ
የለሁም እንደ ሰው
አለሁ እንደ ቤቴ
አለሁ በግድግዳው፡፡
.
በዘመመ አምዷ
በእርቃነ ሆዷ ፣
ጥበቧን ሸንትፋ ቀለማቷን ነትባ
አለሁኝ ትላለች - የህይወቴ አበባ፡፡
እንደ ቤቴ እያለሁ- እንደ ሰው ለመኖር የለሁም ሂጃለሁ ፣
መሰረቴን ንጂ መሰረት ጥያለሁ፡፡
ግና....
ከመናዴ በፊት ህይወት መሰረቴን
ከማርገፌ በፊት ጥበብ ቀለማቴን
ያባቴ ጥዑም ቃል...
"ልጄ ሆይ? ጠቢብ ሁን" ያለኝ ትዝ ይለኛል፡፡
ሳስታውሰው ቃሉ
የጥበብ ኪታቡ - የአባትነት ውሉ ፣
ኪዳኑ ያመኛል
የለኽም፡ የሚል- ድምጽ በቀቀን ሆኖኛል
የለኽም እያለኝ
አለሁኝ ነው መልሴ
በሙት ሥጋነቴ አትሞትም መንፈሴ፡፡
ህይወቴ ግድግዳው ተራቁቶ ቀለሙ፣
ይሄው ተመልከተኝ አለሁ በግድግዳው አለሁ በሰሌዳው፡፡
.
የቤቴ ግድግዳ ህይወቴ ቀለሙ
እሱ ምንም ቢፋቅ እሱ ምን ቢላላጥ ፣
እኔው እያቀለምሁ ፣ እኔው እየቀባሁ፡፡
አለሁ እምላለሁ።
-
አለሁ እንደ ቤቴ ፣ እንደ እኔነቴ፣
ቀለሙ ቢራቆት ግድግዳው ውበቴ
አታሸንፈኝም "ደራሲው ህይወቴ"።
-
ከሰው መሃል ሁኜ በምናቤ ብጓዝ
ወደ ሰው አያለሁ ወደ ራሴ ስጓዝ፡፡
-//-

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 21:48


ነፍስህን በገነት ያኑርልን ለቤተሰቦችህ ለአድናቂዎችህ ለጎደኞችህ ሁሉ መፅናናትን ይስጥልን🙏

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 20:58


https://www.tiktok.com/@tsinatfazilet/video/7374888822519155974?_t=8mnlt7NXglq&_r=1

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 20:21


የአብሮነት ቤተሰቦች እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው አደረሳቹ 🙏

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 20:19


መልካም ቀን
"እውነቱን ተናገር !!!" እውነትን አቁመው
የዝምታ መልሱ ምስጢሩ ከብዷቸው
እሱ
ንጉሥ ቢጠይቅ ዝም
ለሎሌም መልስ የለም
ይገርፉት ጀመረ ይዘው እያዳፉ
ሚያደርጉት ቢያጡ እፊቱ ላይ ተፉ
መስቀል አሸከሙት በቆሰለ አካሉ
ከለሜዳ አልብሰው "ንጉሥ" ተባባሉ
ራቁቱን ሰቀሉት የግፍ ፅዋ ሞልቶ
ወንበዴ ነው አሉት ደግሞ ንጉሥ ቀርቶ
ሰው እንዲህ ሲጨክን ግዑዛን ደንግጠው
ፀሐይም ጨረቃም ጠቆረ ገፃቸው
ከዋክብት ረገፉ መሬት ፍርሀት ዋጣት
ፈጣሪዋን አይታ ምትገባበት ጠፋት
ሙታንም ተነሱ ሲኦል ቅጥሯ ፈርሶ
የአምስት ቀን ተኩሉ መፈፀሚያው ደርሶ
ይህ ሁሉ በአንድ ቀን
ሀሴትና ሀዘን
ሐሰትና እውነት
ግፍና ነፃነት
በዚህ
መስቀልና ጅራፍ ችንካር የሾህ አክሊል
ወዲህ
የገነት ማህተም ተበርብራ ሲኦል
እያነቡ መሳቅ መሳቅም በለቅሶ
በዚች በመልካም ቀን ሁሉም ታየ ደርሶ

           # ሶሊያና

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 20:00


ወዳጄ ሆይ

አንዳንድ ጊዜ አጠገብህ ያሉ ሰዎች የሚፈልጉትን በቀላሉ ሲያገኙና በትምህርት ፣ በሥራ በትዳር ... ቶሎ ስኬትን ሲጨብጡ ታያለህ። አንተ ግን አንድ ቦታ ቆመሃል። ወቅቱ የእነርሱ ነውና ከመቅናት ይልቅ ባገኙት ስኬት የደስታቸው ተካፋይ ሁን። ለእነርሱ ያደረገ አምላክ ላንተም እንደሚያደርግልህ እመን።

ይኸውልህ ፤

🌗የማንጎ ዛፍ የቡርቱካን ዛፍን ከርሱ ወቅት ቀድሞ ምርትን ስለሚሰጥ አይጨነቅም። ስኬት፣ በወቅት የሚታጨድ መኸር ነው፣ወቅትህ ሲሆን ምንም ነገር ከመንገድህ ሊቆም አይችልም። የአንበሳ በዝግታ መራመድ ስንፍናን ወይንም ድካምን አያመለክትም፤ ያለመውን አደን በእጁ ለማስገባት እርምጃውን እያሰላ እንጂ። የሰዎች ፈጥነው መራመድ አያውክህ።

የራስህን ኑሮ ኑር!

ፈጣሪህን ታመን። ልብ በል፤ ቤትህን በፍጥነት ሠርተህ መጨረስህ ሳይሆን ንፋስና ጎርፍን መቋቋም የሚችል ጠንካራ አድርገህ መሥራትህ ነው ቁምነገሩ። በሰዎች ደስታ ደስ ይበልህ። የእውቀት ሰውና ጠንካራ ሠራተኛም ሁን! ደግሞ ሁሉንም አታገኝም!አንተ የተሳፈርክበት አውሮፕላን መሬት ሲያርፍ፣ ከዛ መሬት የሚነሣ አውሮፕላን አለ፤ ሌሎች ደግሞ ለመነሳት በሂደት ላይ ይገኛሉ። ሁሉም መዳረሻቸው የተለያየ ነው፤ ምናልባትም ወዳንተ መነሻ ሊሆን ይችላል። አየህ ህይወት እንዲ ናት፤ "ደረስኩ" ብለህ ስታስብ ሌሎች ያንን ሥፍራ "ጥለው" ሲነሱ ታገኛቸዋለህ። አንዳንዶቹ አንተ ወደ ተነሳህበት፣ ሌሎቹም ወደ ሌላ።

🌗በልጅ ማጣት ምክንያት ቀን ማታ የሚያለቅሱ ሰዎች እንዳሉ በልጆቻቸው ምክንያት ቀንና ማታ የሚያለቅሱ ሰዎች አሉ፣ባል ባለማግባታቸው የሚጨነቁ ሰዎች እንደገጠሙኝ ሁሉ በማግባታቸው የሚጨነቁም ሰዎች ገጥመውኛል። በሥራ እጥረት ምክንያት የታመሙ እንዳሉ በሥራ ብዛት ምክንያት የሚታመሙ አሉ። ልጆቻቸው ፈተና ላይ ጥሩ ውጤት እንዲያመጡላቸው የሚጨነቁ እንዳሉ፣ ልጆቻቸው ጥሩ ትምህርት ቤት እንዲገቡላቸው የሚጨነቁ አሉ።

እናም ወዳጄ

ህይወት እንዲህ ነው፤ በቃ! ሁሉንም የኛ ልናደርግ አንችልም!፣ ንፋስን አባሮ እንደመያዝ ነውና። ሁሉንም ነገር የራስህ እንዲሆን ከመድከም ይልቅ ባለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን ሞክር። ከአንዱ ምእራፍ ወደ ሌላው ምእራፍ እንደሚያሸጋግርህም ፈጣሪህን ታመን። ሁልጊዜም በአምላክህ ደስ ይበልህ! በእምነትም ኑር!

     መልካምነት ለራስ ነውና

      

አብሮነት/Abronet

20 Jan, 19:22


ተማጽኖ
(በእውቀቱ ስዩም)

አቤቱ
የጠፈር ባለቤቱ
በየብስ ነህ፥ በባህር፥ በምድር ነህ በሰማይ?
በቅጡ ለማናውቅህ ፥ በድንግዝግዝ ለምናይ

አቤቱ የፍጥረት አባት
ከሰማኸኝ ምናልባት
ኮረብታውን ሜዳ አድርገው ፤ ኮረኮንቹን አለስልሰው
የፎይታየን አድራሻ፥ ርቀቱን ቀንሰው
አልልህም!

ጽናት ስጠኝ ፤ ብርቱ አድርገኝ! በየርምጃው እንዳይደክመኝ
ከቀንበሮች ሁሉ መርጠህ፥ ምችለውን አሸክመኝ

አቤቱ! የጠፈሮች ሁሉ መስራች
አፈራርቀህ የምትሰጥ፥ መርዶና የምስራች !
ተወስነህ የማትገኝ ፤ በጊዜና በቦታ
ወሰን የሌለህ ዝምታ
እኔ ልጅህ-ሲመቸኝ ፤ ሲመቸኝ አማኝ
ባይመችህም ስማኝ

ካደፈጠው እዳ ሁሉ፥ በየበስ፥ ባየር በቀላይ
ከአውሎ ነፋስም በላይ
ከመሬት መራድም ይልቅ
ሰው ነው ሰውን ሚያሳቅቅ
ሰው ነው የሰው አደጋ
ደግሞ በሌላ ገጹ፥ ሰው ነው ለሰው ልጅ ጸጋ
ከስጦታው አካፍለኝ ፥ ካደጋው አስመልጠኝ
አልሳሳት አልልህም፥ የሚታረም ስህተት ስጠኝ !