Latest Posts from Omo Bank Official (@omobankofficial) on Telegram

Omo Bank Official Telegram Posts

Omo Bank Official
OMO Bank Official
1,855 Subscribers
724 Photos
32 Videos
Last Updated 27.02.2025 04:43

Similar Channels

EthiopianReporterJobs.com
97,039 Subscribers
Hibret Bank
15,372 Subscribers

The latest content shared by Omo Bank Official on Telegram


የባንኩን ስራዎች ውጤታማነት በዘላቂነት ለማስቀጠል በተያዘው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ወደ እንቅስቃሴ የተሰማሩ የባንኩ አመራሮችና ሰራተኞች የለውጡ ግንባር ቀደም አስፈፃሚ ሆነው መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ተገለፀ።

ባንኩ ይህንኑ ስትራቴጂካዊ ውጥን ወደ ዘለቄታዊ ውጤታማነት ለመቀየር ባስቀመጠው አሠራር መሠረት ላለፉት ሁለት ወራት ወደ ተለያዩ ዲስትሪክቶች አሰማርቶ የነበረውን የድጋፍና ክትትል ግብረ-ኃይል አፈፃፀም ሪፖርት በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሆቴል ገምግሟል፡፡
ቀን 13/6/2017 ዓ/ም አዲስ አበባ

የባንኩን የሥራ ክንውኖች ትርጉም ያለው ውጤት ለማስመዝገብ በሚደረገው የለውጥ አስተዳደር ሂደት በተሰጠው ተልዕኮ ላይ የተሠማሩ አመራሮችና ሠራተኞች ግንባር ቀደም የለውጥ መኮንኖች እንደሆኑ በመገንዘብና ከተለመደው አሠራር ወጣ ያሉ አካሄዶችን በመከተል ለባንኩ ሁለንተናዊ ለውጥ መትጋት እንዳለባቸው የዕለቱን የውይይት መድረከ የመሩት የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አብርሃም አላሮ ተናግረዋል፡፡

በዘላቂነት የባንኩን የዕድገትና የባለቤትነት ኃላፊነት በተግባር እየተከታተለ ያለው የመንግስት አካልም ለውጡን ይበልጥ ለማስቀጠል ቁርጠኛ አቋም እንዳለው ከባንኩ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት ውጤታማ ተግባቦት ላይ መድረስ መቻሉን ያስረዱት ፕሬዝዳንቱ ይህንኑ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የለውጡን ግስጋሴ ከወትሮ በተለየ መንገድ መምራት አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በተለይም በስትራቴጂካዊ ድጋፍና ክትትል ወቅት የተገኙ የመረጃ ግብአቶችን የባንኩን ቢዝነስ ስራዎች ትኩረት በሚመጥን መልኩ ተንትኖ በመጠቀም ዓመቱን በተሻለ ውጤታማነት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ፍጥነት መጨመር ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ባለፉት ሁለት ወራት በተደረገው ድጋፍና ክትትል ወቅት የተገኙ ድሎችን ማስቀጠልና ችግሮች ላይ ፈጣን የመፍትሔ እርምጃዎችን የመውሰዱን ኃላፊነት እንደሚሰራም ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል፡፡

በድጋፍና ክትትሉ የተገኙ ተሞክሮችን ለማስቀጠል እና በተለዩ ችግሮች ላይ ፈጣን ምላሾችን ለመስጠት የጋራ አቋም በመያዝ የውይይት መድረኩ ተጠናቋል፡፡

ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!

Dear valued Customers!
Please find lists of Correspondent Banks and their Addresses for your information.

ውድ ደንበኞቻችን!
በአሁኑ ሰዓት ከባንካችን ጋር በትብብር የሚሰሩ የውጭ ሀገራት ባንኮች እና አድራሻቸው እነዚህ ናቸው፡፡

የቁጠባ፣ የብድር ስርጭትና አመላለስ ተግባራትን ወደላቀ ደረጃ ለማድረስና ባንኩን ትርፋማ ለማድረግ ከዲስትሪክት የስራ ኃላፊዎች ጋር በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረገ፡፡

ጥር 17/2017 ዓ.ም አ/አበባ
ኦሞ ባንክ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ አመት የሥራ ዕቅድ አፈፃፀም ሥራዎችን በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ሆቴል ጥር 16 እና 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ከዲስትሪክት የሥራ አመራሮችና የዋናው ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በጋራ ገምግሟል፡፡

በግምገማው የኦፕሬሽን፣ የኮርፖሬት ፋይናንስና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ባንኩ ያለበትን ወቅታዊ ቁመና ላይ የባንኩ አመራሮች በጥልቀት ተመካክረዋል።

ቁጠባን ከማስቆጠብ አንፃር፣ የብድር ስርጭትና አመላለስ ተግባር ላይ በአብዛኛው ቅርንጫፎች ያሉት ሠራተኞች በአንፃራዊነት በሁለተኛው ሩብ ዓመት የተሻለ ውጤታማ ተግባር ስለመፈፀማቸው ሪፖርት ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን፤ በተለይም የማስቆጠብ ስራዎችንና ሌሎችንም ተግባራት ከዚህ በተሻለ በመተግበር ባንኩን ትርፋማ ለማድረግ ሁሉም የባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፍ ቢሮዎች ከዋናው መስሪያ ቤት ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

በተለይም የባንኩን የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን ከማሻሻል አኳያ፣ የውዝፍ ብድር ያለማስመለስ፣ ነባር ደንበኞችን ተከታትሎ ያለማስቆጠብና ሌሎች በ6 ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ የታዩ ክፍተቶች ላይ በስፋት ውይይት የተደረገ ሲሆን በዋናነትም ለለውጥና ለውጤታማነት እንቅፋት በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ ባንኩ በተሻለ አፈፃፀም የተሻለ ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት የተዘጋጀ መሆኑንም ከውይይቱ ለመረዳት ተችሏል፡፡

ከውጤታማነት አኳያ ሁሉንም ሠራተኞች መመዘን አስፈላጊ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፣ ከቀበሌ የደንበኛ ግንኙነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጎ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን በዋናነትም ሥራዎችን በአግባቡ እየተወጡ ምላሾች እስኪሰጡ ድረስ ለለውጥ በትጋት መስራት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ ሁሉም ሠራተኛ ባመጣው ውጤትና ተግባር መሠረት እንደሚታይ ተመላክቷል፡፡

በግማሽ አመቱ ዕቅድ አፈፃፀም ከአጠቃላይ አፈፃፀም አንፃር ሲታይ ከአምናው አንፃር የተወሰኑ መሻሻሎች የታዩ ሲሆን በቀጣይ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በትጋት መስራት እንደሚያስፈልግ የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አብርሃም አላሮ ገልፀዋል፡፡

ባንኩን ለማሳደግ አሁንም ለውጥ ማምጣት ይቻላል ያሉት ፕሬዝዳንቱ ያለንን አቅም በተገቢው መጠቀም አለብን ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ምላሽና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን በቀጣዪም ስድስት ወር የብሄራዊ ባንክ መስፈርትን ጠብቆ መስራት፣ የአይቲ መሰረተ ልማትን ከቴሌ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ማሟላት፣ ሁሉንም አይነት የብድር ገንዘቦችን ማስመለስ፣ በህግ አፈፃፀም ስር ያሉትን ጉዳዮች የማጠናቀቅ ስራ፣ የውስጥ ቁጥጥር ሲስተም ስራዎችን ማጠናከር፣ የዳታ ማጥራት ስራን አጠናክሮ መቀጠል፣ የባንኩን አሴት ማሳደግና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት መስራት እንደሚጠበቅ የባንኩ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል፡፡

በአጠቃላይ ለተሻለ የሥራ አፈፃፀም ስኬትና ውጤታማነት ሁሉም ሠራተኛ የመፍትሄው አካል በመሆን ጥራት ያለውን አገልግሎት በመስጠት ለደንበኛ እርካታ በትጋት መስራት ይጠበቃል ተብሏል፡፡

ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ !

እንኳን ለበዓሉ በሰላም አደረሳችሁ!

የኦሞ ባንክ የማኔጅመንት አባላትና አጠቃላይ የባንኩ ሠራተኞች በሙሉ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ይገልፃሉ፡፡

ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!

ኦሞ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖችን 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ ኢሊሌ ሆቴል ባለአክሲዮኖች በተገኙበት አካሂዷል፡፡

ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
በጠቅላላ ጉባኤው የተለያዩ አጀንዳዎች ቀርበው የውሳኔ ሀሳቦች የተሰጠባቸው ሲሆን ከነዚህም መካከል የአክሲዮን ዝውውር፣ የውጭ ኦዲተር ሪፖርት ማድመጥና የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ተከናውኗል፡፡

በዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ በባንኩ አክሲዮን ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው ባለድርሻዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ያልሆኑና ገለልተኛ አባላት አማካኝነት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ተካሂዷል፡፡

የጠቅላላ ጉባኤውን የመሩት የኦሞ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት ባንኩ ከብሄራዊ ባንክ በተሰጠው የስራ ፈቃድ መሠረት ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ የገባ መሆኑን ተናግረዋል።

አጠቃላይ የዝግጅት ምዕራፉ ተጠናቅቆ ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ/ም የባንክ ሥራውን የጀመረው የኦሞ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤቱን ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ ያዛወረ መሆኑንም አቶ ጥላሁን አስታውሰዋል፡፡

ባንኩ ውጤታማነቱንና ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።
ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!

ኦሞ ባንክ ከወለድ ነፃ የአንድ መስኮች የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ከባለድርሻ አካላትና ፈፃሚዎች ጋር በወልቂጤ ከተማ ውይይት እያካሄደ ነው።

ቀን፦ ህዳር 26/2017 ዓ.ም
ውይይቱ ባንኩ ለመላው ህብረተሰብ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መሆኑ ተመላክቷል።

የአሁኑ ኦሞ ባንክ በማይክሮ ፋይናንስ ደረጃ በ1989 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን ከሰኔ 15/2014 ዓ.ም ጀምሮ ከብሔራዊ ባንክ የባንክ ስራ ፈቃድ በማግኛት እየሰራ የሚገኝ ባንክ ነው። በአሁኑ ሰዓት 241 ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን ከ5 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ይገኛሉ።

ባንኩ የደንበኞቹን የፋይናንስ አገልግሎት ፍላጎት ለማርካት ከወለድ ነፃ የአንድ መስኮት የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

በውይይት መድረኩ የጉራጌ፣ የምስራቅ ጉራጌና የየም ዞን እንዲሁም የማረቆና የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያዎች እና ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የኡለማ ኮሚቴ የመጅሊስ ስብሳቢና የኦሞ ባንክ የስራ ኃላፊዎች፣ የወልቂጤ ዲስትሪክት እና በወረዳና ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች ተሳትፈዋል።
ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!

Our Channels
Website:- www.omobanksc.com
Email: - [email protected]
Facebook: - https://www.facebook.com/OMFIHQ
Instagram: - https://www.instagram.com/omobankofficial
linkedin:- https://www.linkedin.com/in/omobankofficial
Twitter: - https://x.com/omobankofficial
Youtube: - https://www.youtube.com/@omobankofficial

How To Apply:
Interested applicants fulfilling the above requirements are invited to apply within five (5) consecutive days from November 25, 2024 to November 29, 2024, online via below OMO Bank Vacancy Web Portal: https://www.omobanksc.com/jobs/
Apply Here
N.B- Only shortlisted applicants will be contacted and incomplete applications will not be considered.

OMO BANK S.Co Vacancy
OMO Bank would like to invite qualified and competent applicants to apply for the following vacant posts.
1.  Head, Compliance Management  Section
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 8 years of banking experience out of which 2 years working at Senior Risk Management and Compliance Officer.
Required Amount: 01(One)
2.  Head, Risk Management  Section
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 8 years of banking experience out of which 2 years works at Senior Risk Management and Compliance Officer.
Required Amount: 01(One)
3.  Remittance and Forex Officer
Required Qualification and Experience
Qualification: BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management, and any other related fields.
Experience: 4 years Banking Experience from which at least 2 years works at Remittance and Forex Section.
Required Amount: 01(One)
4.  Trade Service Officer
Required Qualification and Experience
Qualification: BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 4 years Banking experience from which at least 2 years works at Trade   service section
Required Amount: 01(One)
5.  Compliance Management  Officer II
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 4 years of banking experience out of which 2 years working at Risk Management and Compliance Officer.
Required Amount: 01(One)
6.  Risk Review Officer II
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 4 years of banking experience out of which 2 years working at Risk Management and Compliance Officer.
Required Amount: 01(One)
7.  Senior Purchase Officer
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 6 years of banking experience out of which 2 years working at purchase Officer.
Required Amount: 01(One)
8.  Procurement officer I
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 2 years of banking relevant experience
Required Amount: 02(Two)
9.  Logistics & supplies officer I
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Banking & Finance, Accounting, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 2 years of banking relevant experience
Required Amount: 01(One)
10.  HR Officer II
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Human Resource Management, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 4 years of banking relevant experience
Required Amount: 01(One)
11.  HR Officer I
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA Degree in Human Resource Management, Business Administration, Economics, Management and any other related fields.
Experience: 2 years of banking relevant experience
Required Amount: 01(One)
12.  Chief Bank Security Officer
Required Qualification and Experience
Qualification:  BA or Diploma /level IV in Police Science, Security Management, Management or Related.
Experience: 8 / 10 years, out of which 4 years works at Police/Military High Ranking Officer/General or Equivalent
Required Amount: 01(One)
Place of Work: For all Vacant Posts Head Office (Addis Ababa)
Salary & Benefits: As per the Bank’s Salary Scale & Benefits Package
Deadline: November 29, 2024.

ኦሞ ባንክ በ4 ወር የሥራ አፈፃፀም ዙሪያ ከ19 ዲስትሪክት ስራ አስኪያጆች ጋር በአዲስ አበባ ራስ ሆቴል ውይይት አካሄዷል።

ቀን 7/03/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
በውይይቱ የባንኩ አመራሮች የተግባር አፈፃፀም ሚናቸውን በአግባቡ በመወጣት የባንኩን እንቅስቃሴ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ 
የባንኩን የሥራ አፈፃፀም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ዲስትሪክቶች ዕቅድ በመንደፍ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሊገቡ እንደሚገባ ተገልፆል።

በሌላ በኩል ደግሞ ኦሞ ባንክ  የቢዝነስ  ተቋም መሆኑን በመገንዘብ ለሁለንተናዊ ዕድገትና ትርፋማ ለመሆን ግብ ተይዞ መስራት ያስፈልጋልም ተብሏል።

በቁጠባ የሚሰበሰበዉን ሀብት በአግባቡ በመምራትና መልሶ ለብድር  ስርጭት አገልግሎት እንዲውል በማድረግ ትርፍን ማዕከል ያደረገ እንቅስቃሴ ላይ ውጤታማ ሥራ መስራት አስፈላጊ  እንደሆነም የባንኩ ኘሬዝዳንት አቶ አብርሃም አላሮ ለስብሰባው ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል።

የመረጃ ማጥራት ሥራን በሚመለከት የሁሉም ዲስትሪክት ማናጀሮች ኃላፊነት በመሆኑ በጥንቃቄና በትጋት መስራት እንደሚያስፈልግም አሰተያየት  ተሰጥቷል።

ባንኩን ውጤታማ ለማድረግ ማንኛውም ውጣ ውረዶች ወደኋላ እንዳይጎትቱን በቁርጠኝነት ወደ ተሻለ ውጤት ላይ ለመድረስ ተግቶ መንቀሳቀስ  እንደሚያስፈልግ የዕለቱን መድረኩ የመሩት የባንኩ ኘሬዝዳንት ተናግረዋል።

አላስፈላጊ ወጪዎችን በመቀነስ ጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ሥርዓትን ወጥ በሆነ መንገድ በመምራትና ማዕከላዊነትን መጠበቅ ከሁሉም  ስራ መሪዎች እንደሚጠበቅ ኘሬዝዳንቱ አሳስበዋል።

አሁን የሚስተዋለውን አንዳንድ የኦፕሬሽን፣ የፋይናንስ አስተዳደር ስርአት፣ ወጪና ገቢን አመጣጥኖ ያለማስኬድ ችግሮችን በአጭር ጊዜ ወደ ውጤታማነት መቀየር ከምንጊዜም በላይ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር እንደሆነ ያሳሰቡት የባንኩ ፕሬዝዳንት ይህንኑ ተግባር አፈፃፀም የሚገመግም የማናኔጅመንት አካላት በተደራጀ መልኩ ወደ ስራ መግባቱና ሁሉም የአመራር አካል በላቀ ትጋትና ቅንጅት ለላቀ ምርታማነትና ለትርፋማነት በህብረት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
                         ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!

Our Addresses
Website:- www.omobanksc.com
Email: - [email protected]
Facebook: - https://www.facebook.com/OMFIHQ
Instagram: - https://www.instagram.com/omobankofficial
linkedin:-  https://www.linkedin.com/in/omobankofficial
Twitter: - https://x.com/omobankofficial
Youtube: - https://www.youtube.com/@omobankofficial

ኦሞ ባንክ የባንኩን መሠረታዊ የኦፕሬሽን ሥራዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ በመምራት ቁልፍ ተግባራቶች ላይ ውጤት ማስመዝገብ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አስገነዘበ ።

ቀን 06/02/2017 ዓ.ም አ/አበባ
ባንኩ ባለፈው ሳምንት ወደ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፍ ቢሮዎች በመሄድ የሶስት ወር የዕቅድ ትግበራ አፈፃፀም እና የባንኩን የሥራ እንቅስቃሴዎች በአግባቡ እንዲመሩ የመለየትና አቅጣጫ የማመላከት ተልዕኮ ይዞ የወረደውን የሥራ መሪዎች የሥራ ሂደት ግምገማን አድምጦ የመፍትሔ ሀሳቦችን እንደ አቅጣጫ አስቀምጧል ።

በዚህ የስራ ስምሪት በዋናነት የተለዩ ስትራቴጂካዊ ችግሮችን ከዘላቂ መፍትሔዎቻቸው ጋር የማስቀመጥ ውሳኔዎችን ያመላከተው የዛሬው ስብሰባ በሚቀጥሉት ቀናት ወደ ተጨባጭ የተግባር ክንውን እንዲሸጋገር ወስኗል ።

ይህንኑ የተግባር ኃላፊነት ወደ ተሻለው ውጤታማ ምዕራፍ ለማሸጋገር እያንዳንዱ የሥራ መሪዎችና ፈፃሚዎች ከተለመደው አካሔድ ወጣ ብለው ማሰብና ስልት መቀየስ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን መድረኩን የመሩት የባንኩ ኘሬዝዳንት አቶ አብርሃም አላሮ ተናግረዋል ።

በተለይም ቁልፍ ተግባራቶችን አቀናጅቶ መምራትና የመፍትሄ ሃሳቦችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት አመራሩ ስትራቴጂ የመንደፉን ሚና እና በተቀናጀ መንገድ እንዲመራም አቅጣጫ ተሰጥቶት ተጠናቋል።

በግምገማ መድረኩ የባንኩ ማኔጅመንት አካላትና የሥራ መሪዎች ተሳትፈዋል ።
ኦሞ ባንክ የሁላችንም ባንክ!