ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

@zemariabelmekbib


Abel Mekbib | Official Channel

@zemari_nabel_mekbib

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

21 Oct, 06:57


የመስቀል ዓይነቶች ክፍል 1

1. የመጾር መስቀል በቅዳሴ እና በማዕጠንት ጊዜ ሠራዒው ዲያቆን የሚይዘው ነው።


2. የእጅ መስቀል ካህናት ምእመናንን የሚባርኩበት በእጅ የሚያዝ የመስቀል ዓይነት ነው።

3. የአንገት መስቀል ምእመናን በክርስቶስ ያላቸውን እምነት ለማመልከት ከማዕተባቸው ጋር በአንገታቸው የሚያደርጉት ነው።

4. እርፈ መስቀል በማንኪያ ቅርጽ ተሠርቶ በእጀታው ላይ የመስቀል ምልክት ያለበት ነው። ሠራዒው ዲያቆን በቅዳሴ ጊዜ የአምላካችንን ክቡር ደሙን ስምእመናን የሚያቀብልበት ነው። እንዲሁም ጌታችን በዕለተ ዓርብ የተወጋበት ጦር ምሳሌ ነው።

Abel Mekbib | Official Channel

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

13 Sep, 04:02


የተዘጋው ደጅ

ከዋልክበት ውለው ፤ ከአዳርህ ያደሩት ፤ደቀ መዛሙርትህ:: በጽኑ ኀዘን ወድቀው ፤ ልባቸው ተነክቶ ፤ በመስቀል በሞትህ:: በአንተ የደረሰ እንዳይደርስባቸው በስጋት ተውጠው ከቤት ውስጥ ዋሉ ፤ አንከፍትም ብለው ፤ በራቸውን ዘግተው::

በተረዳህ ጊዜ ፤ ማንም እንደማይከፍት ፤ የተዘጋውን በር :: በረቂቅ ሥልጣንህ ሳይከፈት ገባህ ‹‹ሰላም ለእናንተ ይሁን›› ብለህ ልትናገር :: ‹‹እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ ፤ ማንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ አገባለሁ››

ብለህ መናገርህ ::

ከቶ ለምን ይሆን በልቤ በር ላይ ጥበቃ መቆምህ? እኔ እንደሆን አልከፍት ዝግ ነው ልቡናዬ መች ሥፍራ አለውና ለአንተ ለጌታዬ!?

ይልቅስ ዛሬም በረቂቅ ሥልጣንህ ወደ ልቤ ግባ እኔም ባልከፍትልህ ሰላም ለአንተ ይሁን በለኝ እባክህን ትንሣኤዬ አድርገው ለእኔም ትንሣኤህን!

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

17 Aug, 07:27


Abel Mekbib | Official Channel

@zemari_nabel_mekbib
https://t.me/zemariabelmekbib

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

15 Aug, 07:35


የብርሃን እናት
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ከፍል ሶስት

እግዚአብሔር ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ለምን እንደፈጠራቸው ሲገልጥ ለምድር ከማብራት ጋር 'ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ' ብሎ ለጊዜ መቁጠሪያ እንዲሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ግዙፍ ፍጥረታት ለሰው ተፈጠሩ እንጂ ሰው ለእነርሱ አልተፈጠረም፡፡

ሊቁ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘአንጾኪያ እንዳለው ፀሐይን ፣ ጨረቃና ከዋክብትን ጣዖት አድርገው እስከማምለክ የሚደርሱ ሰዎችም ሞኞች ሆነው የምናገኛቸው ድርጊታቸው በአሁን ዘመን ቋንቋ ሰው የቤቱን ውስጥ አምፖል ፣ የእጁን ሰዓትና የቀን መቁጠሪያውን አምላኬ ብሎ ቢያመልክ የሚሳቅበትን ያህል ተመሳሳይ ድርጊት ስለፈጸሙ ነው፡፡

ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት ብቻ ሳይሆኑ ፍጥረታት ሁሉ ለሰው የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ፍጥረታት ለሰው ሊታዘዙና ሰውን ሊያገለግሉ ተፈጥረዋል፡፡ ሰው ከፈጣሪው ባይጣላ ኖሮ ፍጥረታትን እንደ ፈለገ ያዝዛቸው ነበር፡፡ ይህን እውነታም ከእግዚአብሔር ጋር የታረቁ ቅዱሳን ሰዎች ተፈጥሮን አዝዘው አሳይተውናል፡፡ ባሕር ለሙሴ ተከፈለ ፣ ፀሐይ ለኢያሱ ፣ ቁራ ኤልያስን መገበ ፣ እሳት ለሠለስቱ ደቂቅ በረደ ፣ አንበሶች ለዳንኤል ትራስ ሆኑ ፣ ዓሣ አንበሪ ለዮናስ ቤት ሆነ፡፡ በዚህም ሁሉም ለሰው የተፈጠሩ መሆናቸውን ነገሩን፡፡

ስማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ ፤ የሰማይም ጠፈር የአጁን ሥራ ያወራል' ፍጥረታት ሌላው ሥራቸው የፈጣሪን ክብር መናገር ነው፡፡ መዝ. ፲፱፥፩ በሦስቱ ወጣቶች መዝሙር ላይ እንደተገለጸው አንደበት ባይኖራቸውም እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ በመኖራቸው ብቻ የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጡ መዘምራን ናቸው፡ ፡ ከኃያልዋ ፀሐይ እስከ ትንሹ ጉንዳን ድረስ ለፈጣሪያቸው ይዘምራሉ፡ : ከዘማሪዋ ወፍ እስከሚያንቋርረው እንቁራሪት ድረስ ፈጣሪያቸውን ያመሰግናሉ፡፡ ለእነዚህ ሁሉ ማሕሌታውያን ፍጥረታት የመዘምራን አለቃቸው የሰው ልጅ ነበረ፡፡

ከእነዚያ ሁሉ ድንቃ ድንቅ ፍጥረታት የበለጠው ፍጥረት በፈጣሪው አምሳል አዋቂ ገዢና ሕያው ሆኖ የተፈጠረው የሰው ልጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር “ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር' ሲል ሰምተው ቅዱሳን መላእክት “እግዚአብሔርን የሚመስል ፍጥረት እንዴት ያለ ነው?' ብለው ሊያዩት የጓጉለት ግሩምና ድንቅ ፍጥረት

ሰው ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ (masterpiece) ፣ መላውን

ህዋ ጠቅልሎ የያዘ ንዑስ ዓለም (microcosm) ፣ ከመላው የከዋክብት ሥርዓት በላይ የተወሳሰበ አእምሮ ያለው ጠቢብ ፣ ሊኖር እንጂ ሊሞት ያልተፈጠረ ንጉሥ ፣ “በእጆችህ ሥራ ሁሉ ላይ ሾምከው' እንደሚል እግዚአብሔር በፍጥረታቱ ላይ የሾመው ገዢ ነው፡፡ መዝ. ፰፥፮

ሰውን እግዚአብሔር በአርኣያውና በአምሳሉ መፍጠሩን ራሱ በቃሉ 'አንፍጠር' ብሎ መስክሮ መናገሩ የሰው ልጅን ከፍጥረታት ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ያደርገዋል፡፡ “ምንትኑ፡ ይከብር ፡ እምዝንቱ፡ አይ፡ ምክሕ ፡ ዘየዐቢ ፡ እምዝንቱ፡ ትምክህት” “ከዚህ ክብር የሚበልጥ ምን ክብር አለ? ከዚህ ትምክህት የበለጠስ ምን የሚያስመካ ነገር አለ?' እንዳለ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ 8

እግዚአብሔር ሰውን ከፍጥረታት ሁሉ በኋላ መጨረሻ መፍጠሩም የክብር እንግዳ ቦታ እንደሠጠው የሚያሳይ ነው፡፡ እንግዳ ከመምጣቱ በፊት ሁሉ ነገር እንደሚዘጋጅ እግዚአብሔር ሰማዩን በከዋክብት አስጊጦ ፣ ምድርን በአበባ አስውቦ ያቆየው በመላእክት አሳጅቦ የተቀበለው “የእግዜር እንግዳ' የሰው ልጅ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም እግዚአብሔር ለፍጥረታቱ ሁሉ የደፋላቸው ዘውድ አክሊለ ፍጥረታት

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

31 Jul, 11:20


ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ pinned «ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Telegram: https://t.me/deaconhenok»

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

31 Jul, 11:20


ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Telegram: https://t.me/deaconhenok

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

31 Jul, 04:03


የዲያቆን ሄኖክ ሃይሌን መፅሐፎች ለማንበብ ከስር ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ

https://t.me/deaconhenok

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

28 Jul, 03:22


የብርሃን እናት ክፍል ሁለት
• የእግዚአብሔር እንግዳ

ንጉሥ ዳዊት

'ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ ጨረቃና ከዋክብትን አንተ የሠራሃቸውን ታስበው ዘንድ ሰው ምንድርን ነው?

ትጎበኘውስ ዘንድ የስው ልጅ ምንድር ነው?'

“አቤቱ፥ እርሱን ታውቀው ዘንድ ሰው ምንድር ነው?

ማወቁ ብቻ ራሱ እኛ የሰው ልጆች ምን ስለሆንን ነው ያሰኛል፡፡ የራሳችንን ጠጉር ሳይቀር በቁጥር ያውቀን ዘንድ እኛ ምንድር ነን? ክፉ ደግ መሥራታችንን በቀንና ሌሊት የሚከታተለንስ ምን ስለሆንን ነው? “ማለዳ ማለዳስ ትጐበኘው ዘንድ፥ ሁልጊዜስ ትፈታተነው ዘንድ ሰው ምንድር ነው?' ኢዮ. ፯፥፲፰

እጅግ ውስብስብና ግዙፋን የሆኑ የእልፍ አእላፋት ከዋክብትና የብዙ ሺህ ፀሐዮች ባለቤት ፣ እኛ የማናውቃቸው የብዙ ፕላኔቶች ፈጣሪ ባለ አጭር ቁመት ባለ ጠባብ ደረቶቹን እኛን ማየቱ ለምን ይሆን? በመጠንዋ ከሌሎች ብዙ ፕላኔቶች ከምታንሰው መሬት ላይ አፈር ዘግኖ የፈጠረውን ደካማ ፍጥረት ለቅጽበት እንኳን ዓይኑን ሳይነቅል መመልከቱ የሰው ልጅ ምን ስለሆነ ነው? ጻድቁ ኢዮብ እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል ፦ የማትተወኝ እስከ መቼ ነው? ምራቄንስ አስክውጥ ድረስ የማትለቅቀኝ እስከ መቼ ነው? ሰውን የምትጠብቅ ሆይ፥ በድዬስ አንደ ሆነ ምን ላድርግልህ? ስለ ምን እኔን ለአንተ ዓላማ አደረግኸኝ? ስለ ምን አኔ ሸክም ሆንሁብህ?” ኢዮ. ፯፥፲፰-፳

በዚህ ደረጃ ከንቱና ታናሽ የሆነው የሰው ልጅ የእግዚአብሔር የትኩረት ማዕከል የሆነበት ምክንያት በኦሪት ዘፍጥረት ላይ እንዲህ

በአጭሩ ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ 'አግዚአብሔር ሰውን ከምድር አፈር አበጀው' ዘፍ. ፪፥፯

ቅዱስ ባስልዮስ እንዲህ ይላል

እግዚአብሔር ሰውን ከምድር አፈር አበጀው' ከሚለው ቃል ውስጥ የሰው ልጅ ኢምንት መሆኑንም ታላቅ መሆኑንም እረዳለሁ፡፡ የተፈጠረበትን አፈር ብቻ ካየህ የሰው ልጅ ኢምንት ነው፡፡ የተፈጠረበትን ክብር ካየህ ግን የሰው ልጅ ታላቅ ነው''

በእርግጥም እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ጨረቃንና

ከዋክብትን የፈጠረበት መንገድ ሰውን ከፈጠረበት ሁኔታ ጋር ሲተያይ

የሰው ልጅ ከሁሉም ታላቅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከብርሃን ጀምሮ

በምድርና ሰማይ ያሉ አካላትን የፈጠረው “ለይኩን' “ይሁን‛ በሚሉ

ይሁንታዎች በቃሉ ተናግሮ ነበር፡፡ ብርሃን ይሁን ሲል ብርሃን ሆነ ፣

ጠፈር ይሁን ሲል ጠፈር ሆነ ፤ የብስ ይገለጥ አለ የብስ ሆነ ፤ ምድር

ዘርን ታብቅል አለ በቀለ ፤ ብርሃናት በሰማይ ይሁኑ አለ ብርሃናት ሆኑ ፤

ውኃ ተንቀሳቃሾችን ታስገኝ አለ ተገኙ ፤ ምድር እንስሳትን ታስገኝ አለ

ተገኙ፡፡

ባሕርን ዓሦችን እንድታወጣ ፣ ምድርን ዕፅዋትን እንድታበቅል በቃሉ ያዘዘው እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ከአፈር ሲፈጥረው ግን “ምድር ሰውን ታብቅል' አላለም፡፡ ከመፍጠሩ በፊት እስካሁን ካደረገው በተለየ ከራሱ ጋር ተነጋገረ “ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን አንፍጠር' በሚል ልዩ የሆነች ምክረ፡ ሠላሴ እግዚአብሔር ከራሱ ተማክሮ ሰውን ሊፈጥር ወደደ፡፡ መላእክቱን በአሳቡ ፣ ሌላውን ፍጥረት በቃሉ የፈጠረው ሁሉን ቻይ አምላክ ሰውን ግን በግብር ሊፈጥር ወድዶ ለአክብሮተ ሰብእ ጭቃ ይዞ ታየ'፡፡

ቅዱስ ባስልዮስ እንዲህ ይላል ፦

ከእኛ በላይ የተዘረጋው ታላቁ ስማይ የተፈጠረው በአግዚአብሔር ቃል ነው፡፡

እንደ ትልቅ የምንቆጥራቸውና ዓይኖቻችንን አንጋጥጠን የምናደንቃቸው ፀሐይ ጨረቃና ከዋክብትም በቃሉ ብቻ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ባሕርና የብስ ፣ እንስሳትም ሁሉ በቃሉ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ከብርሃን በላይ ፣ ከሰማይም በላይ ፣ ከጠፈርም በላይ ፣ ከብርሃናትም በላይ ግን የሰው ልጅ አፈጣጠር የከበረ ነው፡፡

የብርሃን እናት ክፍል ሁለት

ታስብለት ዘንድ የሰው ልጅ ምንድር ነው?' ይላል፡

፡ መዝ. ፰፥፫ ፤፻፵፬፥፫

ንጉሥ ዳዊት የሰማይን ርዝመት ፣ የፀሐይን ርኅቀት ፣ የጨረቃና ከዋክብት ውበትና ብዛት ሲያይ ቁመቱ ከሁለት ሜትር የማያልፈውን ደቃቁን የሰው ልጅ እግዚአብሔር ማስታወሱ ራሱ ደነቀው፡፡ እውነትም እኛ ካለንበት ጋላክሲ ውጪ ያሉትን እጅግ ብዙ ዓለማትና ድንቃ ድንቅ ፍጥረታት አስተውለን በተረዳን ጊዜ እግዚአብሔር ሥፍር ቁጥር ከሌለው ድንቅ ፍጥረቱ ሁሉ ለይቶ እኛን ያስታውሰን ዘንድ እኛ ምንድርን ነን? እንላለን፡፡

እኛን ሊጎበኝ እስከ አሳባችን ድረስ ሊመረምረን መፍቀዱስ የሰው ልጆች ምን ስለሆንን ነው? ጻድቁ ኢዮብ 'ታከብረው ዘንድ ልብህንስ ትጥልበት ዘንድ ሰው ምንድርን ነው?' እንዳለው እግዚአብሔር እኛን

ባሕርን ዓሦችን እንድታወጣ ፣ ምድርን ዕፅዋትን እንድታበቅል በቃሉ ያዘዘው እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ከአፈር ሲፈጥረው ግን “ምድር ሰውን ታብቅል' አላለም፡፡ ከመፍጠሩ በፊት እስካሁን ካደረገው በተለየ ከራሱ ጋር ተነጋገረ “ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን አንፍጠር' በሚል ልዩ የሆነች ምክረ፡ ሠላሴ እግዚአብሔር ከራሱ ተማክሮ ሰውን ሊፈጥር ወደደ፡፡ መላእክቱን በአሳቡ ፣ ሌላውን ፍጥረት በቃሉ የፈጠረው ሁሉን ቻይ አምላክ ሰውን ግን በግብር ሊፈጥር ወድዶ ለአክብሮተ ሰብእ ጭቃ ይዞ ታየ'፡፡

ቅዱስ ባስልዮስ እንዲህ ይላል ፦

ከእኛ በላይ የተዘረጋው ታላቁ ስማይ የተፈጠረው በአግዚአብሔር ቃል ነው፡፡

እንደ ትልቅ የምንቆጥራቸውና ዓይኖቻችንን አንጋጥጠን የምናደንቃቸው ፀሐይ ጨረቃና ከዋክብትም በቃሉ ብቻ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ባሕርና የብስ ፣ እንስሳትም ሁሉ በቃሉ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ከብርሃን በላይ ፣ ከሰማይም በላይ ፣ ከጠፈርም በላይ ፣ ከብርሃናትም በላይ ግን የሰው ልጅ አፈጣጠር የከበረ ነው፡፡

የእኛ ሰውነትን ሙሉ በሙሉ በአጆቹ ያበጃጀው ዘንድ የተገባ ሆነ፡፡ አንዱን መልአክ አንዲያበጃጀን አላዘዘውም፡፡ ምድር ራስዋ እንደ በራሪ ነፍሳት አላበቀለችንም፡፡ የመላእክትን አለቆችም ይህን አድርጉ ያንን ሥሩ ብሎ አላዘዛቸውም፡፡ እንደ ሠዓሊና ቀራጺ በአምላካዊ አጆቹ አፈርን አነሣ፡፡ የተሠራበትን መንገድ ስታይ ስው ክቡር ነው ፤ የተፈጠረበትን አፈር ስታይ ሰው ከንቱ ነው"5

ነቢዩ ዳዊት የፀሐይን የጨረቃንና የከዋክብትን ታላቅነትና ውስብስብ ተፈጥሮ አይቶ ከሰው ታናሽነት ጋር አነጻጽሮ “ታስበው ዘንድ ሰው ምንድርን ነው?' አለ እንጂ ከተፈጠርንበት ክብር አንጻር ስናየው “በአጆችህ የፈጠርከውን የሰውን ልጅ ባየሁ ጊዜ ታስባት ዘንድ ፀሐይ ምንድር ናት? ትጎበኛቸውስ ጨረቃና ከዋክብት ምንድር ናቸው? የሚያሰኝ ክብር ለሰው ልጅ ተሠጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር ብዙ ከዋክብትን ቢፈጥርም አንዳቸውም ምንም እውቀት የላቸውም፡፡ ፀሐይ ምን ብትገዝፍ ከትልቅ የእሳት ኳስነት ያለፈ ሕያውነት የላትም፡፡ ከሩቅ አምራ ተውባ ለብዙኃን ብታበራም ማን እንደሆነች እንደምታበራ እንኳን አታውቅም፡፡


የብርሃን እናት ከፍል 2
ይቀጥላል

ዘማሪ አቤል መክብብ ቻናል

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

17 Jul, 03:47


ቅዱስ ቶማስ

ስም ፥ ዲዲሞስ፣ ቶማስ አጠራር ፥ ትንሣኤ ሙታንን ከማያምኑ/ ከሰዱቃውያን

ዕረፍት : ቆዳው ተገፍፎ መታሰቢያ ፥ ግንቦት 26

አጠራር

ትንሣኤ ሙታን የለም ብለው ከሚያምኑ ከሰዱቃውያን ወገን ነበር።

“የችንካሩን ምልክት”

ሐዋርያት የጌታችንን ትንሣኤ ሲነግሩት ፣ የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም"ያለ ነው።

“ጌታዬ አምላኬ"

ኋላም በዝግ ቤት ጌታችን ተገልጦ የጌታችንን ችንካሩን ምልክት እና ጎኑን ዳስሶ “ጌታዬ አምላኬ” ብሎሞ ተናገረ ፣አመነ።

(९ 20:25)

መስኮትን የዳሰሰች እጅ

ጌታችንን የዳሰሰችው እጁ በሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ትገኛለች፡፡

ሰማዕትነት ቆዳው ተገፍፎ ሰማዕትነትን ተቀብሎ አርፏል፡፡ በረከቱ ይደርብን።


ዘማሪ አቤል መክብብ ቻናል

ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል መክብብ

28 Jan, 23:31


Channel created

3,932

subscribers

8

photos

0

videos