ቀን:- 11/02/2017ዓ.ም
በአ.አ ከተማ መርካቶ አካባቢ ከቆርቆሮ እና ከኮነቴነር ቤቶች አቅራቢያ ወዳለው ' ነባር የገበያ ማዕከል (ህንጻ) ' የተዛመተው እሳት የህንጻውን አንደኛውን ክፍል ክፉኛ አውድሞታል።
እስካሁን ሰው ላይ ስለደረሰ ጉዳት ሪፖርት አልተደረገም።
በትላንት ምሽቱ የእሳት አደጋ ምንም እንኳን ይፋዊ የጉዳት መጠን ባይገለጽም የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው።
በርካቶች ብዙ የደከሙበት ንብረታቸው በአንድ ምሽት ወደ አመድነት ተቀይሯል።
ምን ያህሎቻችን ነን ግን ለነገ አብዝቶ የሚያስጨንቀን?
ይኼው ነው!።
ክፉ አታምጣብን
ሰላም አውለህ ሰላም አሳድረን በሉ/እንበል/
ፎቶ ፦ ' መርካቶ ሸማ ተራ ' ከትላንት ምሽቱ አስከፊና ከባድ የእሳት አደጋ በኃላ ዛሬ ላይ ከላይ በፎቶው የምትመለከቱትን ይመስላል።