Pharma College Shashemene Campus

@pharmacollegeshashemenecampus


Pharma College Shashemene Campus Official Telegram Channel

Pharma College Shashemene Campus

16 Jul, 15:15


Loading...

Pharma College Shashemene Campus

27 Jun, 16:59


#MoE

ትናንት የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና "የቴክኒክ ችግር" አጋጥሞት እንደነበር ትምህርት ሚኒስቴር አረጋገጠ።

ስለሆነም ፈተናውን በድጋሜ እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰአት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ይሰጣል ተብሏል።

ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በየተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንድትወስዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

@tikvahuniversity

Pharma College Shashemene Campus

10 Apr, 10:30


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ ፣

እንኳን ለኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ ፋርማ ኮሌጅ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
ዒድ ሙባረክ!

Pharma College Shashemene Campus

16 Feb, 06:54


For pharma college students
Exit exam schedule for management/ Business management in Hawassa university is on Monday yekatit (February) 11/2016 E.c

Pharma College Shashemene Campus

16 Feb, 06:52


For Pharma college students
Exit exam schedule for Accounting and finance dep is on yekatit (February) 09/2016 E.c. in Hawassa University

Pharma College Shashemene Campus

04 Feb, 12:53


Share Letter_on_Model_Exam_for_Private_HEIs[1].pdf

Pharma College Shashemene Campus

31 Jan, 19:03


የመውጫ ፈተና ተራዘመ።

የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ መራዘሙን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትምህርት ሚኒስቴር ማረጋገጥ ችሏል።

የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም።

ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ይፋ ባደረገው መርሐግብር ፈተናው ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል።

ለአዲስ ተፈታኞች ሞዴል ፈተና ከጥር 27 እስከ 30/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የተፈታኞች ዝርዝር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚላክም ተገልጿል።

Via @tikvahuniversity

@tikvahethiopia

Pharma College Shashemene Campus

25 Jan, 01:52


#ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ 20/2016ዓ.ም መራዘሙን ስለማሳወቅ

በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመፈተን የምዝገባ ጊዜው ጥር 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 15/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ መጠቀሱ የሚታወሰ ነው።

ይሁን እንጂ በተፈታኞች ጥያቄ መሰረት የምዝገባ ጊዜው እስከ ጥር 20/2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ሌሎች ሁኔታዎች ግን ቀደም ሲል በተገለጸው አግባብ የሚከናወኑ መሆኑን እናሳውቃለን።

=========================
የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለምትፈተኑ አመልካቾች በሙሉ

ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ስለሆነም በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተናውን ተፈትናችሁ ያላለፋችሁ እና ከጥር 27 - የካቲት 1/ 2016 ዓ.ም ድረስ የመውጫ ፈተናውን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተፈታኞች በሙሉ ምዝገባ የምታካሂዱትና የመፈተኛ ተቋም (የመንግስት ዩኒቨርሲቲ) የምትመርጡት ከታች በተገለጸው ማስፈንጠሪያ (Link)
(https://exam.ethernet.edu.et)
ስለሆነ፣ ከጥር 08 እስከ ጥር 20 2016 ዓ.ም ድረስ የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በቴሌ ብር ብቻ በመክፈል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

አመልካቾች ተጨማሪ ድጋፍ የምትፈልጉ ከሆነ በስልክ ቁጥር +251 118 13 21 76 ወይም በኢሜይል [email protected] በኩል ድጋፍ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ

ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የምታካሂዱት እና የአገልግሎት ክፍያ የምትፈፅሙት በተቋማችሁ በኩል መሆኑን እየገለጽን አስፈላጊው የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማችሁ የሚደርሳችሁ መሆኑን እናሳውቃል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ

Pharma College Shashemene Campus

24 Jan, 11:29


This guide provides detailed steps for registering for the national re-exit exam
https://exam.ethernet.edu.et/registration_guide_exitexam.pdf

Pharma College Shashemene Campus

17 Jan, 12:19


#MoE

ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም #አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ላሉ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል ብሏል።

በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተናውን ተፈትነው ያላለፉ እና ከጥር 27 - የካቲት 1/ 2016 ዓ.ም ድረስ የመውጫ ፈተናውን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ተፈታኞች በሙሉ ምዝገባ የሚያካሂዱት የመፈተኛ ተቋም (የመንግስት ዩኒቨርሲቲ) የሚመርጡት በዚህ ማስፈንጠሪያ (Link)
(https://exam.ethernet.edu.et)  ነው።

ስለሆነ ከጥር 08 እስከ ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በ " ቴሌ ብር " ብቻ በመክፈል መመዝገብ እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

አመልካቾች ተጨማሪ ድጋፍ የሚፈልጉ ከሆነ በስልክ ቁጥር +251 118 13 21 76 ወይም በኢሜይል [email protected] በኩል ድጋፍ ማግኘት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የሚፈቱ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚያካሂዱትና  እና የአገልግሎት ክፍያ የሚፈፅሙት በተቋማቸው በኩል መሆኑን ገልጾ አስፈላጊው የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማቸው በኩል እንደሚደርሳቸው አመልክቷል።

@tikvahethiopia

Pharma College Shashemene Campus

17 Jan, 12:19


#ጥምቀት

" በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን አይወክሉም " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው በተለያዩ ቋንቋዎች ለተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቃለ መጠይቅና ምላሽ እንዲሰጡ ለተመረጡ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በሰጡት አባታዊ መመሪያ የቅድስት ቤተክርስቲያን መልእክት የሚተላለፈው በማእከል በመሆኑ የማእከሉን መልእክት ብቻ እንዲያስተላልፉ መመሪያ የሰጡ ሲሆን ከግል አስተያየት መቆጠብ እንደሚገባም አበክረው አሳስበዋል።

ቤተክርስቲያኗ የሰላም ሰባኪ እንደመሆኗ መጠን የቤተክርስቲያን መልእክት ሲተላለፍ ሰላም ላይ ማተኮርና በዓል ለማክበር የሚወጡ ምእመናን በዓሉ በሰላም አክብረው እንዲመለሱ መልእክት ማስተላለፍ እንደሚገባ ግልጽ መመሪያ ሰጥተዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያዊ ሁሉም ሃይማኖቶች ተከባብረው የሚኖሩባት ሀገር መሆኗ ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ይህ በዓል የሚከበርባቸውን ቦታዎች ለማጽዳትና ሥርዓት ለማስከበር ጥረት እያደረጉ ያሉ የሌሎች ሃይማኖት አባላትን በአባትነት ያመሰገኑት ብፁዕነታቸው ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች የሚገኙ የሌሎች ቤተ እምነቶችን ማክበር እንደሚገባ ለሁሉም ካህናትና ምእመናን አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፈ ያለውን የበዓል አከባበር ክልከላን የሚገልጹ የሐሰት ዜናዎች ቤተክርስቲያንን የማይወክሉና ቤተክርስቲያናችን በዓሉን በሰላም ለማክበር ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እያደረገች ያለውን ጥረት ከግንዛቤ ያላስገባ መሆኑን ብፁዕነታቸው አሳውቀዋል።

#EOTCTV

@tikvahethiopia

Pharma College Shashemene Campus

23 Dec, 15:49


Pharma College attended the 1st Belt and Road Chinese university and overseas partner exchange conference organized by MalishaEdu. The conference took place from December 14-15, 2023 in Guangzhou, China. During the conference, the College signed a comprehensive Memorandum of Understanding (MOU) with Wuhan Institute of Technology (WIT), a provincial public university in Wuhan, Hubei, China. The institute, founded in 1972, is affiliated with the Province of Hubei and sponsored by the provincial government.

Our College also had the opportunity to engage with various Chinese, African, and Asian universities, as well as ambassadors and diplomats based in China. This was a unique opportunity for the College's staff, students, partners.