ዴቪድ ዴሄያ " ጎል ሳይቆጠርብን መውጣት መቻላችን ለኛ ጠቃሚ ነገር ነው በተለይም በሜዳችን በሆነ ጨዋታ በጥሩ ሁኔታ ተከላክለናል ብዙ ለውጥ አላደረግንም እንደኔ ሀሳብ ለማሸነፍ የሚረዱንን በቂ እድሎችን ፈጥረናል ነገር ግን ጨዋታው ከጥሩ ቡድን ጋር እንደመጫወታችን የተዘጋጋ ጨዋታ ሆኖብናል ከዚህ የተሻለ ውጤት ይገባን ነበር በእያንዳንዱ ልምምድ ላይ ራሳችንን ለማሳደግ, በመከላከሉ የተሻለ ለመሆንና በጥምረት ለመስራት እንሞክራለን ስለዚህ የተለማመድነውን ተግብረን ጎል ሳይቆጠርብን መውጣታችን ትልቅ ነገር ነው በመከላከሉ በዚሁ ከቀጠልን ጨዋታዎችን ለማሸነፍ እንችላለን
ራሽፎርድ 2 ወይም 3 ምርጥ እድሎችን አጊንቶ በእነሱ ግብ ጠባቂ ከሽፎበታል ማሸነፍ ይገባን ነበር ጨዋታው መጠናቀቂያ አከባቢ ጎል ለማስቆጠር ጥሩ ጊዜ ነበር ነገር ግን የመጨረሻዋ ሰከንድ እስከምትደርስ ድረስ ጎል ለማስቆጠር ሞክረናል።