Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

@akakikaltycom


ይህ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ገፅ ነው!

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

22 Oct, 19:08


ስራ ለሌላቸው የኮሪደር ልማት ተነሺ ነዋሪዎች የስራ እድል ለመፍጠር የክ/ከተማ አስተዳደሩ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሆነ ተገለፀ።

ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም (አቃቂ ቃሊቲ )

በ2ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ምክንያት ከካሳንቺስ ተነስተው ወደ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 10 አሰተዳደር የመጡና ስራ የሌላቸው ነዋሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ እንዲሰማሩ ለማስቻል ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ፣ ውብና ተመራጭ ለማድረግ በ2ኛ ዙር በኮሪደር ልማት ከካሳንቺስ ተነስተው ልማቱን ደግፈው ወደ ክ/ከተማው ለመጡ የልማት ተነሺ ነዋሪዎች በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል።

በዛሬው ዕለትም ከካሳንቺስ ተነስተው ወደ ክ/ከተማው የመጡና ስራ የሌላቸው ነዋሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ ስልጠና ወስደው ወደ ስራ እንዲሰማሩ ለማስቻል ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መርሃግብር ተከናዉኗል።

የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ውቢት ዮሐንስ እንዲሁም የወረዳ 10 አስተዳደር ዋና ስራ አሰፈፃሚ በመድረኩ ተገኝተው ለነዋሪዎቹ የእንኳን በደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ አስተዳደሩ ወደ ክ/ከተማው ለመጡ የልማት ተነሺዎች አካባቢያቸውን ፅዱ፣ ውብና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ ከሚሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ጎን ለጎን ስራ ለሌላቸው ነዋሪዎች በመረጡት የስራ ዘርፍ ስልጠና ሰጥቶ ወደ ስራ እንዲሰማሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

ወ/ሮ ዉቢት አያይዞም የልማት ተነሺዎቹ በአካባቢዉ ያለዉን ፀጋ ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎችን ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን አሟጦ በመጠቀም ለነዋሪዎቹ የስራ ዕድልና ለኑሮ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በልዩ ትኩረት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም የምዝገባ መስፈርቶችን በማሟላት ስራ ፈላጊ ነዋሪዎች ከሚቀጥለው ሰኞ ጥቅምት 18/ 2017ዓ.ም ጀምሮ በአቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና እንደሚጀምሩ ተገልፀዋል።

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በርካታ ስራ የሌላቸው የልማት ተነሺ ነዋሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በአስተዳደሩ እየተደረገላቸው ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

22 Oct, 11:53


ባለስልጣኑ በ6.2 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባቸውን የ15 አቅመ ደካማ ነዋሪ ቤቶች አስመርቆ አስረከበ።
==========================
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም (አቃቂ ቃሊቲ )

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፍቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 06 በ6.2 ሚሊየን ብር ወጪ ያሳደሳቸውን 15 የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ሰርቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቶቹ አስረክቧል።

በቤት ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ሚጀና ፣ የክ/ከተማው ም/ዋና ስራ ስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ውቢት ዩሀንስ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ያብባል አዲስ ፣ የከተማው አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ደሳለኝ ተረፈ  ፣ የወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል ገ/ፃዲቅ በተገኙበት ተካሂዷል።

የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለማየሁ ሚጀና በርክክቡ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ቤቶቹን ላደሱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው ቤቶቹ ከመታደሳቸው በፊት ለሰው ልጅ መኖሪያነት የማይመቹ  ነዋሪዎቹ በአቅም ማጣት ለዓመታት  በጉስቁልና በቤቶቹ ሲኖሩ የነበሩና መሆናቸውን በማንሳት አሁን ላይ ቤቶቹ በአጭር ጊዜ በፍጥነት ለመኖር በሚያጓጓ መልኩ መታደሳቸውን በመግለፅ ሌሎች ተቋማት ከዚህ ልምድ በመውሰድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እስክትሆን ለዜጎች ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ያብባል አዲስ በከተማዋ መንግስት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማስተባበር በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ በመጥቀስ በዛሬው ዕለት ታድሰው ለነዋሪዎች የተላለፉት ቤቶች የዚሁ ተግባር ማሳያ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የከተማው አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ደሳለኝ ተረፈ ከለውጡ ማግስት በተከናወኑ ሰው ተኮር ስራዎች የበርካታ ዜጎች ህይወት እየተለወጠ እንደሚገኝ በማንሳት በወረዳው የተደረገው ድጋፍ እርስ በርስ መረዳዳት ከተቻለ የበርካታ ዜጎችን ህይወት መቀየር የሚቻል መሆኑን ያረጋገጠ መሆኑ ማሳያ ነውና ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

22 Oct, 11:49


ጥራት ያለው የወተትና የእንቁላል ምርት ከገበያ ባነሰ ዋጋ ከእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል እያገኙ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም (አቃቂ ቃሊቲ)

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘዉ የእንስሳት ልማትና የልህቀት ማዕከል ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኙ መሆኑን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ማዕከሉ በልማት የተነሱ አርሶ አደሮችን በዘላቂነት ከማቋቋም ባሻገር ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ በማቅረብ የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድ አወንታዊ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የማዕከሉ ኃላፊ ዶ/ር ፀጋ ለማ ገልፀዋል።

በልማትና ልህቀት ማዕከሉ የከብት ማድለብ፣ የእንቁላል ዶሮ እርባታ፣ የወተት ላምና በማርባት እንቁላል በ8 ብርና አንድ ሊትር ወተት በ75 ብር እና ሌሎች የእንስሳት ተዋጽኦ እንደሚያቀርቡ ኃላፊው ተናግረዋል።

በማዕከሉ ተገኝተው በመሸመት ላይ የነበሩ ነዋሪዎችን አግኝተን እንዳነጋገርናቸው የእንቁላልና የወተት ምርት ከመደበኛ ገበያው ባነሰ ዋጋ ጥራት ያለው ምርት እያገኙ መሆኑን ገልጸው አቅርቦት ላይ በቀጣይ የማስፋት ስራ ቢሰራ ሲሉ ጠይቀዋል።

በእንስሳት ልማትና የልህቀት ማዕከል ምርት ለገበያ በማቅረብ ገበያ ከማረጋጋት ባሻገር ለበርካታ ነዋሪዎች የስራ እድል መፈጠሩን ሲገልፁ 104 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ እንደሚገኙና በሌሎች የስራ ዘርፎችም ለበርካታ ነዋሪዎች የስራ እድል መፈጠሩን ኃላፊው ጠቁመዋል።

ተጨማሪ ማዕከላት በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት በከተማ አስተዳደሩ እቅድ እንደተያዘ የተናገሩት ዶ/ር ፀጋ ምርት ለነጋዴ እንዳይደርስ አሰራር ተዘርግቷል ሲሉ አስረድተዋል።

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

21 Oct, 14:43


#ከነዋሪዎች_አንደበት!

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

19 Oct, 11:55


#ሳምንቱ_በአቃቂ_ቃሊቲ
ጥቅምት 09/2017 ዓ.ም

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

07 Oct, 12:41


አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሰየሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲያገለግሉ ሰይመዋል።

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

07 Oct, 12:41


ተማሪ ያስሚን ከድር የማበረታቻ እና የዉጪ የትምህርት እድል ስኮላርሺፕ ከክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተበረከተላት።

በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ቡልቡላ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2016 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ600ው 570 ውጤት ያመጣችው ተማሪ ያስሚን ከድር በዛሬዉ እለት ከክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የማበረታቻ ሽልማት እና የዉጪ የትምህርት እድል የስኮላርሺፕ ሽልማት ተበርክቶላታል።

ተማሪ ያስሚን በዝግጅት ክፍላችን በኩል ቀርባ በእቅድ ማጥናቷ፣ የወላጆችና መምህራኖቿ ድጋፍ ለዉጤት እንዳበቃት ተሞክሮ ማካፈሏ ይታወሳል።

መስከረም 27/2017 ዓ.ም (አቃቂ ቃሊቲ)